.

.
ዋና ገጽ » » "ጥያቄአለኝ?". ምኔ ነዉ ክርስቲ ያን?

"ጥያቄአለኝ?". ምኔ ነዉ ክርስቲ ያን?

Unknown (በዲያቆን ንጋቱ አበበ) Wednesday, December 24, 2014 | 1:50 PM



¤በአንገቴ ላይ መስቀሉን ከማህተቡ ጋር አስሬ ክርስቶስን እየሰበኩ ምግባሬ እምነቴን ካልገለፀዉ ምኔ ነዉ ክርስቲያን?
¤
ክርስቲያን ተብዬ ድራፍት ቤቱን ያጨናነኩት ረቡእ አርብን ሽሬ ስጋ እያማረጥኩ ከተሰለፍኩ ምኔ ነዉ ክርስቲያን?


¤
በየመጠጥ ቤቱ በየጭፈራዉ ቦታ 'እሱ ጣጣም የለው...' ተብዬ የምገኘዉ ማህተቤን አሰዳቢ ከሆንኩ ምኔ ነዉ ክርስቲያን??
¤
ኦርቶዶክስ እኮ እስክባል ከጫቱ ቅጠል፣ ከትንባሆዉ ጢስ ካልራኩ የድፍረቴ ጥጉ መብቴ እስኪ መስለኝ / በር ድረስ እያጨስኩ ስደርስ ብቻ ረግጬዉ ከገባው ምኔ ነዉ ክርስቲያን??
¤
የከተራዉ የደመራዉ የበአላቱ ቀንነጠላዬን ለብሼ፣/እሱንም በሰበብ/ ስለ ታቦት ብጠየቅ ስለ መስቀል ስጠየቅ መልስ ካልሰጠዉ?
¤
የፀሎት መፀሃፍ በአይነቱ መፀሃፍ ቅዱስ በብዛት ደርድሬ ለመግለጥ ግን ከሰነፍኩ..
¤
አስቀዳሽ ጿሚ ተብዬ ቅዱስ ስጋዉን ክቡር ደሙን ተቀብዬ ቤቴ ስገባ አንደበቴን ለስድብ ከከፈትኩ ምኔ ነዉ ክርስቲያን??
¤
በቅዱስ ቃሉ ማህተብ በስርአተ-ተክሊል ትዳር መስርቼ ሚስቴን ከሰደብኩ፣ከመታው፣ከፈታሁ ምኔ ነዉ ክርስቲያን?
¤
ድንግል እናቴን አማላጅ ብዬ ካሉኝ ሁሉ ቀናት ሰንበትን መስጠት አቅቶኝ የእመብርሃንን ታምሯን ካልሰማዉ ምኔ ነዉ ክርስቲያን?
¤
በሃይማኖታዊ በአላት ቅዱሳን በሚከብሩበት ቀን በአለም ሞቅታ ተስቤ ለፆም መያዣ/መፍቻ በሚል ሰበብ ከሰከርኩ፤ከዘሞትኩ ምኔ ነዉ ክርስቲያን?
¤
የዝማሬዉ ካሴት ከአለሙ ዘፈን ጋር ደርድሬ ለምርጫ ስቸገር የቅዱሳኑን ስእል ከአለም ሰዎች ጋር ለጥፌ ለመስገድ ስጨነቅ ምኔ ነዉ ክርስቲያን??
¤
አገልጋይ ተብዬ ///ቤት ገብቼ በሰከረ አንደበት ለምስጋና ስነሳሳበ በወንዴም በእህቴ ላይ ቂም ይዤ ከወረብኩ ምኔ ነዉ ክርስቲያን??
¤
ነጠላ ለብሼ ለመማር ወጥቼ ከሴት/ከወንድ ጋር የቅድስትቤ/ አጥር ተደግፌ በሴሰነኝነት ከታወርኩ ምኔ ነዉ ክርስቲያን??
¤
እንከን የሌለባት አባቶቼ በጸናት ያቆይዋትቅድስት / ያስተማረችኝን ካልኖርኩበት ኦርቶዶክስ እኮ ተብዬ ስሟን ካጎደደፍኩ ምኔ ነዉ ክርስቲያን?

0 comments:

Post a Comment

Note: Only a member of this blog may post a comment.

ቤተልሔም ዘተዋሕዶ

በኦርቶዶክሳዊት
ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ ለሚነሱ ማንኛውም ጥያቄ መልስ
ለመስጠት የሚሰራ ብሎግ ነው። ያለዎትን ጥያቄና አስተያየት ይላኩልን።
ቅዱሳትመጻህፍትን አገላብጠን፤ አበው ሊቃውንትን ጠይቀን፤ ያገኘነውን
መልስ ወደእናንተ እናደርሳለን!!!

"የዕጣኑም ጢስ ከቅዱሳን ጸሎት ጋር ከመልአኩ እጅ በእግዚአብሔር ፊት ወጣ" ራዕ 8፤4

"የዕጣኑም ጢስ ከቅዱሳን ጸሎት ጋር ከመልአኩ እጅ በእግዚአብሔር ፊት ወጣ"       ራዕ  8፤4

አዘጋጅ፦ ዲያቆን ንጋቱ አበበ

አዘጋጅ፦ ዲያቆን ንጋቱ አበበ

ቤተልሔም ዘተዋሕዶን ላይክ በማድረግ በፌስቡክ ይከታተሉ

በሳምንት ጊዜ ውስጥ ብዙ የተነበቡ

.