.

.
ዋና ገጽ » » ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል

ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል

Unknown (በዲያቆን ንጋቱ አበበ) Friday, December 26, 2014 | 10:54 AM


የአግዚአብሔር መልአክ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል አናንያ አዛርያ ሚሳኤል ወደአሉበት ወረደ:: የአሳቱን ነበልባልም መታው አሱም አንደነፋስ ቀዘቀዘ የአሳቱም ነበልባል ምን ምን አልነካቸዉም ለመዉታትም አላስቸነካቸዉም:: ያንጊዜም ፫ ሰዎች ስድራቅ ምስሃቅ አብድናጎ በአንድ ቃል አመሰገኑት ባረኩት:: የአባቶቻቺን አምላክ አግዚአብሔር ይባረክ ይመስገን አያሉ:: ስቡህም አሱ ነው ልዑልም አሱ ነው:: ናቡከደነፆርም ሲያመሰግኑ በሰማቸው ጊዜ አደነቀ ፈጥኖ ተነስቶ ቆመና አሺከሮቹን አንዲህ ብሎ ጠየቃቸው አስራቸሁ ከአሳቱ ጉድጉአድ የታላቹሃቸው ፫ ሰዎች አልነበሩም:: ንጉሥ ሆይ አዎን አሉ ንጉሱም አንዲህ አለ አኔ አራት ሰዎች ከአስራት ተፈተው በአሳት መካከል ሲመላለሱ አየሁ የነካቸዉም ነገር የለም:: አራተኛዉም ፊቱ የግዚአብሄር ልጅ ይመስላል:: ከዚህም በኃላ
ናቡከደነፆር ወደምነደው አሳት ጉድጉአድ በር ሄዶ የልዑል አግዚአብሔር አገልጋዮች ስድራቅ ምስሃቅ አብደናጎ ወደዚህ ኑ ዉጡ አለ:: ስድራቅ ምስሃቅ አብድናጎ ከአሳቱ ጉድጉአድ መካከል አፈፍ አፈፍ ብለው ወጡ:: ያን ጊዜም መቁአንንቱ ሹማምንቱ የንጉሡ አለቆች ሁሉ ተሰበሰቡ:: ያን ጊዜም ሰዎቹን አካላቸዉን አሳት አንዳልነካቸው አዩዋቸው የራሳቸዉን ጠጉር አንዳለበለበው የፍታቸዉም መልክ አንዳልጠቆረ የጢስ ሸታ አንኩአን አንደሌለባቸው አዩአቸው:: ናቡከደነጾር ለምድርና ለሰማይ ንጉሥ ለአግዚአብሔር በፊታቸው ሰገደ:: አሁንም የምወዳችሁ ወንድሞቼ ሆይ አምላካቼን ኤግዚአብሄርን አንለምነው ምንም በፊቱ ብንበድል አሱ በደላችንን ይሰዉራልና ስለ ድካማቸንም ይታገሳልና:: ያለዉን ሁሉ ትወዳለህ ከፈተርከውም ሁሉ ምንም ምን ቸል የምትለው የለም ብሎ መክብብ አንደተናገረ:: ዳግመኛም ሁሉን መፍጠርህና መግዛትህ ሁሉን ይክር አንድጥል ታደርግሃለች ብሎ አንደተናገረ ይህን ሊቀ መላአክት ቅዱስ ገብርኤልን ይልክልን ዘንድ በዚህም በወድአኛዉም ያድነን ዘንድ:: ፫ቱ ወጣቶች ስድራቅ ምስሃቅ አብደናጎን ከምነድ አሳት ጉድጉአድ አንዳዳናቸው ያለትህትና ስራ አይፈፀምምና:: ትህትናስ ስራዉን ሁሉ ለማስፈጸም ምድር ናት ብሎ መጽሐፍ አንደተናገረ ዳግመኛም ለአፋቼን ሐሰት መናገርን አናስለምድ አንዳለ:: ዳዊትም ሐሰት የአመፅ አራስ ነው ብሎ አንደተናገረ ዳግመኛም አቤቱ በጥላህ ስር ማን ያድራል ብሎ መንፈስ ቅዱስን በጠየቀ ጊዜ (ለባልንጀራው) ምሎ የማይከዳ ነው አለ:: በወንጌልም የማይረባ ነገር የሚናገር ሁሉ ይፈረድበታል ተብሎ ተነገረ:: ሁላቸንም በክርስቶስ አደባባይ ፊት አንመርምር ዘንድ አለንና ፀሎቱና በረከቱ አገልጋዩን ይጠብቀው ለዘለዓለሙ አሜን:: ምንጭ ድርሳነ ገብርኤል

0 comments:

Post a Comment

Note: Only a member of this blog may post a comment.

ቤተልሔም ዘተዋሕዶ

በኦርቶዶክሳዊት
ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ ለሚነሱ ማንኛውም ጥያቄ መልስ
ለመስጠት የሚሰራ ብሎግ ነው። ያለዎትን ጥያቄና አስተያየት ይላኩልን።
ቅዱሳትመጻህፍትን አገላብጠን፤ አበው ሊቃውንትን ጠይቀን፤ ያገኘነውን
መልስ ወደእናንተ እናደርሳለን!!!

"የዕጣኑም ጢስ ከቅዱሳን ጸሎት ጋር ከመልአኩ እጅ በእግዚአብሔር ፊት ወጣ" ራዕ 8፤4

"የዕጣኑም ጢስ ከቅዱሳን ጸሎት ጋር ከመልአኩ እጅ በእግዚአብሔር ፊት ወጣ"       ራዕ  8፤4

አዘጋጅ፦ ዲያቆን ንጋቱ አበበ

አዘጋጅ፦ ዲያቆን ንጋቱ አበበ

ቤተልሔም ዘተዋሕዶን ላይክ በማድረግ በፌስቡክ ይከታተሉ

በሳምንት ጊዜ ውስጥ ብዙ የተነበቡ

.