መጽሐፍ ቅዱስን ማወቅ ጤናማ ትውልድን ለማፍራት ያስችላል። ሰዎች በሥር ዓት እንዲኖሩ፤ ኃይማኖታቸውን ጠብቀው ዘለዓለማዊ መንግሥትን እንዲወርሱ፤ ከጦርነት ይልቅ ሰላምን ከጥላቻ ይልቅ ፍቅርን እንዲያስቀድሙ እና ገንዘባቸው እንዲያደርጉ፤ አምላካችን ጌታችን እና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለምን ሰው መሆን እንዳስፈለገው እና በከሳሽ ዲያብሎስ እርሱም በቀደመው ሰይጣን አጥተነው
የነበረውን ልጅነት እንዴት እንዳስመለሰልን እንዲያውቁ ወ.ዘ.ተ ያስችላል። በብሉይ ኪዳን ዘመን በታላላቅ ነብያት የተጻፉት የትንቢት ቃሎች ፍጻሜ ያገኙበት መሆኑም በሰፊው የተጠቀሰበት ክፍል ነው። በአጠቃላይ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ይህን ዓለም እንዴት አሸንፈን በአዳም ስህተት ያጣነውን የክብር ቦታ ደግመን እንድናገኝ፤ በኃጢአት ምክንያት ከደረሰብን የሞት ቅጣት ወደ ዘላለማዊ ሕይወት የምንገባበትን መንገድ እንዳሳየን የምንረዳበት ክፍል ነው።
የነበረውን ልጅነት እንዴት እንዳስመለሰልን እንዲያውቁ ወ.ዘ.ተ ያስችላል። በብሉይ ኪዳን ዘመን በታላላቅ ነብያት የተጻፉት የትንቢት ቃሎች ፍጻሜ ያገኙበት መሆኑም በሰፊው የተጠቀሰበት ክፍል ነው። በአጠቃላይ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ይህን ዓለም እንዴት አሸንፈን በአዳም ስህተት ያጣነውን የክብር ቦታ ደግመን እንድናገኝ፤ በኃጢአት ምክንያት ከደረሰብን የሞት ቅጣት ወደ ዘላለማዊ ሕይወት የምንገባበትን መንገድ እንዳሳየን የምንረዳበት ክፍል ነው።
ተከታተሉን....
0 comments:
Post a Comment
Note: Only a member of this blog may post a comment.