.

.
ዋና ገጽ » » ነገረ ሃይማኖት

ነገረ ሃይማኖት

Unknown (በዲያቆን ንጋቱ አበበ) Wednesday, December 24, 2014 | 1:24 PM


ሃይማኖት የሚለው ቀጥተኛ ትርጉሙ እምነት ማለት ሲሆን ይኸውም የነገረ መለኮትን ትምህርት; የአምልኮትን ሥርዓት ከእምነትም የተነሣ የሰውን አካሄድ ያጠቃልላል 2ኛ ጢሞ 4:7:: በተጨማሪም ሃይማኖት ማለት እግዚአብሔርን አውቀን በእውነትና በትክክል መንገድ ተመርተን የምናመልክበት ነው ምክንያቱም በሃይማኖት ያለው መንገድ ፈጽሞ የማይለወጥና ፍጹም የሆነ የማያረጅ; የማይቀየር እና እንከን የሌለበት ዘለዓለማዊ እውነት መንገድ ነው:: ይህንንም ሃይማኖት ያስተማረን እርሱ የሚታዩትንና የማይታዩትን ፍጥረታትን በሙሉ ካለመኖር ወደ መኖር የፈጠረ ከመላእክት ከሊቃነ መላእክት ከአጋእዝትና ከሥልጣናት ከኪሩቤልም ከሱራፌልም በላይ የሚኖር: እርሱም
ከፍጥረት ሁሉ አስቀድሞ የነበረ ከምስጋና ሁሉ በላይ ልዑል የሆነ አምላካችን እግዚአብሔር ነው:: አምላካችን ያስተማረን እውነተኛይቱ ሃይማኖት አንዲት ብቻ እርሷም ተዋሕዶ ናት ኤፌ 4:5:: ተዋሕዶ ስንል አምላክ የሰው የሆነበት ሰውም አምላክ የሆነበት ምስጢር የተከናወነበት የተፈጸመበት ነው:: ዮሐ 1: 1-14:: እግዚአብሔር በአንድም በሌላም መንገድ ያስተምረናልና ሲነግረንም ሲያስተምረንም የማይለወጠውን የማይሻረውን የሃይማኖት ፍሬ በሕይወታችን ይዘን እንድንሄድ የሚያስተምሩን; ከሃይማኖት ፈቀቅ እንዳንል የሚመክሩን አባቶችን በየዘመኑ እያስነሣ በሥነ ፍጥረት: በነቢያት: በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ: በመንፈስ ቅዱስና በቅዱሳት መጽሐፍት አስተምሮናል:: በሃይማኖት ከኖርን መላ ሰውነታችን ለእርሱ እናስገዛለን; እንቀደሳለን: ኑሮአችን በሙሉ ይባረካል:: " እናንተ ግን ወዳጆች ሆይ ከሁሉ ይልቅ በተቀደሰ ሃይማኖታችሁ ራሳችሁን ለማነጽ እየተጋችሁ በመንፈስ ቅዱስም እየጸለያችሁ ወደ ዘለዓለም ሕይወት የሚወስደውን የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ምሕረት ስትጠባበቁ በእግዚአብሔር ፍቅር እራሳችሁን ጠብቁ" ይሁ 1:20:: ይህ የሚያስረዳን የሚያስተምረን የሚያረጋግጥልን በተቀደሰ እውነት ውስጥ የመኖር ጥበብ የሚገኘው በሃይማኖት መሆኑን ብቻ ነው:: ለዚህም ነው ካህኑ በቅዳሴ ማርያም ላይ አቤቱ ሁሉን ለፈጠርክ; ለማትታይ አምላክ ለአንተ ሰውነታችንን እንዘረጋለን: ሁሉን ለምታዋርድ ለአንተ ራሳችንን እናዋርዳለን: ሁሉን ለምታሰግድ ለአንተ እንሰግዳለን: ሁሉን ለምትገዛ ለአንተ እንሰግዳለን ሲሉ ዲያቆኑ ደግሞ በፍርሃት ሆናችሁ ለእግዚአብሔር ስገዱ ይላል ሕዝቡም ተቀብሎ አቤቱ በፊትህ እንሰግዳለን እናመሰግንሃለንም ብለው ይሰግዳሉ:: በተቀደሰ እውነት አና ሕይወት ውስጥ በሃይማኖት መኖር ማለት በእንደዚህ አይነት መልኩ ሲኖር ብቻ ነው::

0 comments:

Post a Comment

Note: Only a member of this blog may post a comment.

ቤተልሔም ዘተዋሕዶ

በኦርቶዶክሳዊት
ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ ለሚነሱ ማንኛውም ጥያቄ መልስ
ለመስጠት የሚሰራ ብሎግ ነው። ያለዎትን ጥያቄና አስተያየት ይላኩልን።
ቅዱሳትመጻህፍትን አገላብጠን፤ አበው ሊቃውንትን ጠይቀን፤ ያገኘነውን
መልስ ወደእናንተ እናደርሳለን!!!

"የዕጣኑም ጢስ ከቅዱሳን ጸሎት ጋር ከመልአኩ እጅ በእግዚአብሔር ፊት ወጣ" ራዕ 8፤4

"የዕጣኑም ጢስ ከቅዱሳን ጸሎት ጋር ከመልአኩ እጅ በእግዚአብሔር ፊት ወጣ"       ራዕ  8፤4

አዘጋጅ፦ ዲያቆን ንጋቱ አበበ

አዘጋጅ፦ ዲያቆን ንጋቱ አበበ

ቤተልሔም ዘተዋሕዶን ላይክ በማድረግ በፌስቡክ ይከታተሉ

በሳምንት ጊዜ ውስጥ ብዙ የተነበቡ

.